ምንጭ፡ የጀርመን ድምጽ (Sep. 2, 2024)
«ሁሉም ሰው ፊቱ ጠቁሯል።ስለችግሩ አልቅሼ ብናገር ደስተኛ ነኝ።መንግስት ሰራተኛ ነኝ ለመኖር ተቸግሬ ነው ያለሁት።»ካሉ በኋላ፤ስደት ሁሉ እያሰብን ነው ያለን አሁን።በጣም ተቸጋግረን ማለት ነው።ያለው «ሪያሊቲ» ይህ ነው።»ብለዋል አንድ የክልሉ ነዋሪ ችግሩን ሲያስረዱ ።
በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በመንግስት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የሚካሄደውን ግጭት ተከትሎ ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን አንዳንድ የክልሉ ነዋሪዎች ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል። ነዋሪዎቹ እንደሚሉት በአካባቢያቸው ወጥቶ መግባት እና መደበኛ ሥራዎችን ማከናወን ፈተና ከመሆኑ ባሻገር፤ በትራንስፖርት እና በጤና አገልግሎት ችግር ሰዎች ለሞት እየተዳረጉ ነው።